በብልሹ አሰራር፣በስነ-ምግባር ምንነትና ሙስናን...

image description
- recent news   

በብልሹ አሰራር፣በስነ-ምግባር ምንነትና ሙስናን መታገል ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ።

ብልሹ አሰራርና ሙስናን መታገል ለተቋም ግንባታ ጎልህ ሚና እንዳለው ተገለፀ።
***
     ታህሳስ 15/2018 (ሰ/ፀ/አስ/ቢሮ)

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ለማእከል ሰራተኞች፣ለክ/ከተማ አስተባባሪዎችና ቡድን መሪዎች በብልሹ አሰራር፣በስነ-ምግባር ምንነትና ሙስናን መታገል ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰላም አምሳሉ እንዳሉት የዚህ ስልጠና ዋና ዓላማ ሙስናንና ብልሹ አሰራር ላይ በከተማውና በክ/ከተማ ያሉ ሰራተኞች በየጊዜው አቅማቸውን በማሳደግ የሙስናን መከላከል ትግሉን ማጠናከር ነው ብለዋል። 

ስልጠናውም ሙስናን ከመከላከልና ከማስጠበቅ አኳያ በስራ ላይ ስነ-ምግባር፣ምንነት የስነ ምግባር ጉድለት የሚያስከትላቸው ጉዳቶች፣የሙያ ስነ-ምግባር፣መሠረታዊ መርሆዎችን የሚዳስስ ሰነድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር  የስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮምሽን ከፍተኛ የስልጠና ባለሙያ የሆኑት አቶ ደረጄ ግርማ አብራርተዋል። 

በስልጠናውም የማእከል ሰራተኞች የክ/ከተማ አስተባባሪዎችና ቡድን መሪዎች ተሳትፈዋል።

በመጨረሻም ከተሳታፊዎች የተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎችን ሰፊ የሆነ ውይይት ተደርጎበታል።